08. የኢትዮጵያ የቅጅና ተዛማጅ መብቶች ጥበቃ ማሻሻያ አዋጅ

nty

ሰኔ 29, 2023

የቅጅና ተዛማጅ መብቶች ጥበቃ ማሻሻያ አዋጅን ማሻሻል ያስፈለገበት ዋናኛው ምክንያት በየወቅቱ እያደገ የመጣውን የቅጅና ተዛማጅ መብቶች ጥበቃ እንቅስቃሴ የሚመጥን የህግ ስርዓት ለመዘርጋት እና ባለመብቶች በተደራጀና በተጠናከረ አግባብ መብቶቻቸውን ማስተዳደር የሚችሉበትን ሁኔታ ለመፍጠር ታስቦ ነው፡፡

ይህ የማሻሻያ አዋጅ “የቅጅና ተዛማጅ መብቶች ጥበቃ ማሻሻያ አዋጅ ቁጥር 872/2007” በመባል ይታወቃል፡፡ የአዋጁ ማሻሻያ በዋናነት ያካተተው የጋራ አስተዳደር ማህበር አመሰራረት፣ ሮያሊቲ የመክፈል ግዴታና የሮያሊቲ አሰባሰብ ጋር የተያያዙ ጉዳዮችን ነው፡፡